የካሜሩን ገበሬዎች ወተት እያመረቱ ሀገሪቱ ግን አሁንም የወተት ተዋጽኦዎችን ከውጭ የምታስገባው ለምንድነው? ጋዜጠኛው ያብራራሉ
11:31 11.08.2026 (የተሻሻለ: 11:34 11.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የካሜሩን ገበሬዎች ወተት እያመረቱ ሀገሪቱ ግን አሁንም የወተት ተዋጽኦዎችን ከውጭ የምታስገባው ለምንድነው? ጋዜጠኛው ያብራራሉ
ካሜሩን በዓመት የ120 ሺህ ቶን የወተት እጥረት ያለባት ሲሆን የሀገር ውስጥ ዓመታዊ ፍላጎት ከ300 ሺህ ቶን በላይ እንደሚበልጥ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። ይህ ክፍተት የወተት ዱቄት እና ሌሎች የወተት ተዋጽኦዎችን ከውጭ በማስገባት ይሸፈናል።
ቀዝቃዛ የወተት ማጓጓዣ ሰንሰለት አለመኖር ለእጥረቱ ዋና መነሻ ሲሆን ይህም ወተቱ ለተጠቃሚው ከመድረሱ በፊት በከፊል እንዲባክን ወይም እንዲበላሽ እንደሚያደርግ ኤዲ ጁኒየር አዪሲ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።
አዪሲ መንግሥት ማከናወን ያለባቸውን ጉዳዮችም ጨምረው ገልጸዋል፦
በምርት አካባቢዎች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ማረጋገጥ፣
የምርት አካባቢዎችን በገበሬዎች ከሚተዳደሩ የወተት ማከማቻ ማዕከላት ጋር ማገናኘት፣
ገበሬዎችን ከከተማ ገበያዎች ጋር ማገናኘት፣
ለሀገር ውስጥ ወተት ቅድሚያ መስጠት (በመንግስታዊ ካፌዎች ውስጥ፣ በሆስፒታሎች ወዘተ)።
እ.ኤ.አ በ2024 እስከ 2035 የሚዘልቅ እና ግምታዊ በጀቱ 537.6 ሚሊዮን ዶላር የሆነ የዘርፉ የልማት ዕቅድ መጽደቁን መገናኛ ብዙኃኑ ጠቁመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X