አሜሪካ ለዩክሬን በምታደርገው ድጋፍ እስከ 2030 ድረስ ያለ ጃቭሊን ፀረ-ታንክ ሚሳኤል እንደማይኖራት ተገለጸ
11:00 11.08.2026 (የተሻሻለ: 11:04 11.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
አሜሪካ ለዩክሬን በምታደርገው ድጋፍ እስከ 2030 ድረስ ያለ ጃቭሊን ፀረ-ታንክ ሚሳኤል እንደማይኖራት ተገለጸ
እ.ኤ.አ ከ2022 እስከ 2024 የተደረገው ተጨማሪ ትዕዛዝ ከአምራቾች የማምረት አቅም በላይ በመሆኑ፤ አሜሪካ የጃቭሊን የፀረ-ታንክ ሚሳኤል ክምችቷን ቢያንስ እ.ኤ.አ እስከ 2030 ድረስ መመለስ እንደማትችል የፔንታጎን የበጀት ሰነዶች ይፋ አድርገዋል።
እ.ኤ.አ ከ2022 እስከ 2025 ባሉት ዓመታት የአሜሪካ ጦር ክምችቱን ለመተካት 9 ሺህ 374 ሚሳኤሎችን የገዛ ቢሆንም ርክክቦች የሚጀምሩት ውሉ ከተፈረመ ከበርካታ ዓመታት በኋላ ነው።
በ2024 በጀት የወጣለት የመጨረሻው ዙር የ944 ሚሳኤሎች ግዢ የሚጀምረው በነሐሴ 2030 ሲሆን ርክክቡም በበርካታ ዓመታት ተከፋፍሎ የሚከናወን ይሆናል።
የአንድ ጃቭሊን ሚሳኤል ሙሉ ግዢ እና የማምረት ሂደት እስከ 4.5 ዓመታት፤ የተወንጫፊ መቆጣጠሪያው ደግሞ ከ4 ዓመታት በላይ የሚወስድ በመሆኑ በፍጥነት መተካቱን የማይቻል ያደርገዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X