- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል። አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ይህ ፕሮግራምም ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

የሳህል ህብረት ስልታዊ የሉዓላዊነት እንቅስቃሴ፦ የቀጠናዊ ኃይልን ትርጉም እንደገና መበየን

የሳህል ህብረት ስልታዊ የሉዓላዊነት እንቅስቃሴ፦ የቀጠናዊ ኃይልን ትርጉም እንደገና መበየን
ሰብስክራይብ

“ካፒታሊዝም [የምዕራቡ] በመሰረታዊነት የተመሰረተው በኢኮኖሚ ብዝበዛ ላይ ነው [...] አሁን የቀድሞ የፈረንሳዪ ቅኝ ግዛቶች "የቅኝ ግዛት መገበያያን" አንጠቀምም ባሉ ጊዜ የነዚህ አፍሪካ ሀገራት መሪዎች እስከ ፖለቲካዊ ግድያዎች ድረስ ገጥሟቸዋል። ምክንያቱ ደግሞ "የቅኝ ግዛት መገበያያዎች" ለአውሮፓውያኑ የአመት ገቢያቸው ነው፣ የአፍሪካን ገበያ የሚቆጣጠሩበት ነው” ሲሉ በፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንዳለ ንጉሴ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

የዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ዝግጅታችን በቀዳሚነት ወደ ቀጠናዊ ሉዓላዊነት ቁርጠኛ ሽግግር እያደረገ ወደሚገኘው የሳህል ቀጠና ይወስደናል። ለዚህም በፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የዲፕሎማሲና ዓለም አቀፍ ግንኙነት መምህር እንደለ ንጉሴ አነጋግረናቸዋል። ድረም ኦቭ ቼንጅስ በሁለተኛው ጉዳዩ፣ የሀገርበቀል የሰላም ጥረቶች ተምሳሌት የሆነው የኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር መድረክ አፍሪካዊ ችግሮችን በአፍሪካዊ መፍተሄዎች ከመፍታት አንፃር የሚኖረዉን ትርጉም እንቃኛለን። ለዚህም የፌዴራል ጥናቶች ተመራማሪና የምክክር ሂደቱ ተሳታፊ ኃይለኢየሱስ ታዬ (ዶ/ር)እና የሐይማኖት መምህር እናየምክክር ሂደቱ ተሳታፊ ቀነዐ ለሚን እንግዳ አድርገናል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0