ታንዛኒያ የወተት ተዋጽዖ ዘርፍን እና የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን ለማሳደግ የ231 ሚሊዮን ዶላር ዕቅድ ይፋ አደረገች

ሰብስክራይብ

ታንዛኒያ የወተት ተዋጽዖ ዘርፍን እና የአየር ንብረት ለውጥን የመቋቋም አቅምን ለማሳደግ የ231 ሚሊዮን ዶላር ዕቅድ ይፋ አደረገች

ይህ የ10 ዓመት ፕሮጀክት ከ700,000 በላይ የሚሆኑ የከብት አርቢዎችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሎ እንደሚጠበቅ የእንስሳት እና ዓሣ ሀብት ሚኒስቴር የምርት እና የገበያ ልማት ዳይሬክተር የሆኑት ስቴፈን ማይክል በዓለም አቀፍ የግብርና ኤግዚቢሽን ላይ ተናግረዋል።

 

“ምርታማነትን ለማሳደግ እና ለውጭ ገበያ የሚቀርብ ትርፍ ወተት ለማምረት ዓልመናል” ማለታቸው በአካባቢው ሚዲያ ተዘግቧል።

ዋና ዋናዎቹ ፕሮጀክቱ ዓላማዎች፡-

የወተት ምርትን ማሳደግ እና ታንዛኒያን የወተት ተዋጽዖዎችን በስፋት ወደ ውጭ ከሚልኩ ሀገራት ተርታ ማሰለፍ።

የገበያ ትስስርን ማሻሻል፣ ወጪዎችን መቀነስ እና ለወተት አምራቾች እና አቀነባባሪዎች ከምርት በኋላ የሚደርሰውን ብክነት መቀነስ።

የተሻሻሉ የከብት ዝርያዎችን፣ የተሻለ የውሃ እና የግጦሽ አቅርቦትን ማበረታታት እንዲሁም የበሽታ መከላከያን ማጠናከር።

ℹ ታንዛኒያ በአሁኑ ወቅት በዓመት 13 ቢሊዮን ሊትር ወተት ፍላጎት እያላት የምታመርተው 4 ቢሊዮን ሊትር ወተት ብቻ ነው። ይህም በምርታማነት እና በእሴት ሰንሰለት ልማት ላይ ቀጣይነት ያለው ኢንቨስትመንት እንደሚያስፈልግ ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0