ደቡብ አፍሪካ በአፓርታይድ ላይ የተካሄደውን ታሪካዊ የሴቶች ሰልፍ 70ኛ ዓመት አከበረች

ሰብስክራይብ

ደቡብ አፍሪካ በአፓርታይድ ላይ የተካሄደውን ታሪካዊ የሴቶች ሰልፍ 70ኛ ዓመት አከበረች

የደቡብ አፍሪካ የሴቶች ቀን (ብሔራዊ የሴቶች ቀን) በየዓመቱ ነሐሴ 3 ይከበራል።

ቀኑ እ.ኤ.አ በ1956 20 ሺህ ጥቁር ሴቶች የእንቅስቃሴ ነፃነት የሚገድበውን የአፓርታይድ የይለፍ ሕግ ለመቃወም፤ በሀገሪቱ የአስተዳደር መዲና ፕሪቶሪያ ወደሚገኘው የዩኒየን ሕንፃ ያደረጉትን የሴቶች ሰልፍ የሚዘክር ነው።

"ሴቶች እኩል ክፍያ እንዲሁም በፖለቲካና ንግድ ዘርፍ እኩል ውክልናን በመጠየቅ ነባራዊውን ሁኔታ ለመቀየር በመድፈራቸው እንደ ኅብረተሰብ ተራምደናል" ሲሉ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ዋና ፀሐፊ ምባሉላ ፊኪሌ ተናግረዋል።

የተቃውሞ ሰልፉ አፓርታይድን ለመጣል በተደረገው ትግል ጉልህ የሆነ ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።

"ዛሬ በሁሉም ቦታ ያሉ ሴቶችን ጥንካሬ፣ ጽናት፣ ስኬቶች እና አስተዋፅኦዎች እናከብራለን" ሲል የደቡብ አፍሪካ መንግሥት በመግለጫው አስታውቋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0