የሴኡታ ቀውስ እንዳይደገም ቀጣዩን ድንገተኛ አደጋ ከመቆጣጠር ያለፈ ሥራ ያሻል - ሞሮኳዊ ባለሙያ
16:23 09.08.2026 (የተሻሻለ: 16:24 09.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሴኡታ ቀውስ እንዳይደገም ቀጣዩን ድንገተኛ አደጋ ከመቆጣጠር ያለፈ ሥራ ያሻል - ሞሮኳዊ ባለሙያ
"ከሁሉም በላይ የሴኡታ እና የመሊላን የቅኝ ግዛት ወረራ ለማክሰም ያለመ ሰላማዊ የፖለቲካ ሂደት ያስፈልጋል" ሲሉ ሰኢድ ባካሊ አፅንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።
ባለሙያው ለዘላቂ መፍትሔ የሚያስፈልጉ ያሏቸው ዋና ዋና እርምጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
የቅኝ ግዛት ወረራን ማስቆም፦ "የአውሮፓን ድንበሮች ወደ ውጭ ከማሸጋሸግና በወታደራዊ ኃይል ከመጠበቅ ይልቅ፤ በእኩልነትና በጋራ መከባበር ላይ የተመሰረተ እውነተኛ የሞሮኮ-ስፔን ትብብር መፍጠር።"
ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ችግሮችን መፍታት፦ የሥራ ዕድሎችን በመፍጠርና ፍትሐዊ የሀብት ክፍፍልን በማረጋገጥ፤ የወጣቶችን የሥራ አጥነት እና የትምህርት ማቋረጥ ችግር መቅረፍ።
ድንበርን ብቻ ሳይሆን ተጎጂዎችን መጠበቅ፦ ለስደተኞች ሰብዓዊ እርዳታ፣ ሕጋዊ ከለላ መስጠት እንዲሁም ከዘረኝነት እና ሰብዓዊ ክብርን ከሚነኩ አያያዞች መጠበቅ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X