ከአዲስ አበባ ፈጣን የከተሜነት ዕድገት ጋር የሚመጣጠን ዘመናዊ ግንባታ
14:25 09.08.2026 (የተሻሻለ: 14:34 09.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ከአዲስ አበባ ፈጣን የከተሜነት ዕድገት ጋር የሚመጣጠን ዘመናዊ ግንባታ
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን በአዲስ አበባ ሁለገብ የመኖሪያና የንግድ ሕንፃ ለመገንባት ከዩናይትድ አረብ ኢምሬቶች ሪፖርታጅ ግሩፕ ጋር የቤት ልማት ፕሮጀክት አስጀምሯል።
ስለፕሮጀክቱ የተሰሙ ቁልፍ መረጃዎች፦
▪ከአፍሪካ ኅብረት ዋና መሥሪያ ቤት ፊት ለፊት ይገነባል፣
▪በ23 ሺህ ካሬ ሜትር ቦታ ላይ ያርፋል፣
▪1,086 አፓርትመንቶች፣ የንግድ ማዕከልና የመዝናኛ ሥፍራዎች ይገነባሉ፣
▪በሦስት ዓመታት ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ ታቅዷል።
የመከላከያ ሠራዊት ፋውንዴሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሜጀር ጄኔራል ደረጀ መገርሳ፤ “ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ ፈጣን የከተሜነት ዕድገት ጋር የሚመጣጠን ዘመናዊ ግንባታ ይሆናል” ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X