ማሊ ልመናን ለማስቀረት የሚያስችል አዲስ ብሔራዊ ስትራቴጂ አፀደቀች
19:40 08.08.2026 (የተሻሻለ: 19:44 08.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ማሊ ልመናን ለማስቀረት የሚያስችል አዲስ ብሔራዊ ስትራቴጂ አፀደቀች
መርኃ-ግብሩ "በቅድመ-መከላከል፣ በእንክብካቤ እና በአካታች አቀራረብ" ለሕፃናት ጥበቃ እንደሚሠራ መንግሥት በሰጠው መግለጫ አጽንኦት ሰጥቷል።
አቀራረቡ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነው፡
ለሰው ልጅ ክብር፣
የቤተሰብ፣ የሕብረተሰብ እና ተቋማዊ ባለድርሻ አካላትን ማብቃት።
ለስትራቴጂው ትግበራ እ.ኤ.አ ከ2026 እስከ 2028 የሚቆይ የድርጊት መርኃ-ግብር ተነድፎለታል።
የመገናኛ ብዙኃን እ.ኤ.አ በ2025 ባወጡት መረጃ መሠረት፤ የሕፃናት ልመና ማሊን ጨምሮ በማዕከላዊ ሳኅል ሰፊ ችግር ሲሆን ለልመና ከሚገደዱ ከ20 ሺህ በላይ ሕፃናት ውስጥ 43% የሚሆኑት ሴቶች ናቸው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X