የሳኅል ሀገራት ጥምረት፤ ለናይጄሪያ ፕሬዚዳንት 'የሳኅል የደህንነት ሁኔታ ተንዷል' አስተያየት ምላሽ ሰጠ
18:51 08.08.2026 (የተሻሻለ: 18:54 08.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሳኅል ሀገራት ጥምረት፤ ለናይጄሪያ ፕሬዚዳንት 'የሳኅል የደህንነት ሁኔታ ተንዷል' አስተያየት ምላሽ ሰጠ
"በማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ሪፐብሊክ ያለው የደህንነት ችግር ፈተናዎቻችንን እያባባሱ ይገኛሉ" ሲሉ ቦላ ቲኑቡ ባለፈው ሐሙስ ተናግረዋል።
የቡርኪና ፋሶ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የጥምረቱን ምላሽ አቅርበዋል፦
▪ ሦስቱ ሀገራት "የውስብስብ ሁኔታውን አጠቃላይ ሸክም በጎረቤት ሀገራት ላይ ከመጫን" ይልቅ፤ የደህንነት ሁኔታው በተሻለ እና በትክክለኛ መንገድ እንዲቀርብ ይመኙ ነበር ሲሉ ዣን ማሪ ትራኦሬ አሳስበዋል።
▪ እንደነዚህ ያሉት ንግግሮች "በታሪክ፣ በጂኦግራፊ እና በወንድማማችነት በተሳሰሩ ሕዝቦች መካከል ቅሬታን" የመፍጠር አደጋ አላቸው።
▪ እነዚህ አስተያየቶች "የኒጀር ጦር ለዓመታት ቦኮ ሃራምን በመዋጋት የከፈለውን መስዋዕትነት የናቁ" ናቸው።
የናይጄሪያ ኤምባሲ ጉዳይ አስፈጻሚ መልዕክቱን በመቀበል፤ ለአቡጃ ባለሥልጣናት ሪፖርት እንደሚያደርጉ ገልጸዋል።
በተጨማሪም የሳኅል ሀገራት ጥምረት አባላት ሽብርተኝነትን በመዋጋት ረገድ ለሚያደርጉት ጥረት እውቅና ሰጥተው፤ የጋራ ስጋቱን በውይይት እና በአጋርነት መጋፈጣቸውን አድንቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X