በአዲስ አበባ ያልተጠናቀቁ ሕንፃዎችን የሚያከራዩ አከራዮች የ100 ሺሕ ብር ቅጣት እና የወንጀል ተጠያቂነት ይጠብቃቸዋል
17:16 08.08.2026 (የተሻሻለ: 17:24 08.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በአዲስ አበባ ያልተጠናቀቁ ሕንፃዎችን የሚያከራዩ አከራዮች የ100 ሺሕ ብር ቅጣት እና የወንጀል ተጠያቂነት ይጠብቃቸዋል
የእሳትና አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ያዘጋጀው አዲስ የአደጋ ሥጋት ደኅንነት መመሪያ ወደ ሥራ ገብቷል።
በመመሪያው የተካተቱ ክልከላዎች፦
በሕንፃ ግንባታ ወቅት የሠራተኞች ደኅንነት መጠበቂያ መስፈርቶችን አለማሟላት፣
ለአደጋ የሚያጋልጡ የተቆፈሩ ጉድጓዶችን አለመከለልና ምልክት አለማድረግ፣
ለአደጋ የሚያጋልጡ ጠንካራ ያልሆኑ የማደላደያ ቁሳቁሶችን መጠቀም፣
በቀላሉ ሊደረመስ የሚችል አፈርና የግንባታ ተረፈ ምርቶችን ማከማቸት።
እርምጃው ግንባታቸው ሳይጠናቀቅና የደኅንነት ማረጋገጫ ሳያገኙ ለአገልግሎት የሚውሉ ሕንፃዎች በዜጎች ሕይወትና ንብረት ላይ ከፍተኛ አደጋ ከመደቀናቸው ጋር ተያይዞ የመጣ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X