ቤኒን ከኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ልምድ ለመቅሰም ፍላጎቷን ገለጸች፤ ኢትዮጵያም ተሞክሮዋን ለአፍሪካ ሀገራት ለማጋራት ዝግጁ ነኝ ብላለች

© telegram sputnik_ethiopiaቤኒን ከኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ልምድ ለመቅሰም ፍላጎቷን ገለጸች፤ ኢትዮጵያም ተሞክሮዋን ለአፍሪካ ሀገራት ለማጋራት ዝግጁ ነኝ ብላለች
ቤኒን ከኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ልምድ ለመቅሰም ፍላጎቷን ገለጸች፤ ኢትዮጵያም ተሞክሮዋን ለአፍሪካ ሀገራት ለማጋራት ዝግጁ ነኝ ብላለች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.08.2026
ሰብስክራይብ

ቤኒን ከኢትዮጵያ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ልምድ ለመቅሰም ፍላጎቷን ገለጸች፤ ኢትዮጵያም ተሞክሮዋን ለአፍሪካ ሀገራት ለማጋራት ዝግጁ ነኝ ብላለች

የቤኒን ዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና ኢኖቬሽን ሚኒስትር ማሁና አክፕሎጋ ከኢትዮጵያ አቻቸው በለጠ ሞላ ጋር ባደረጉት ውይይት፤ “የአፍሪካ ሀገራት በኢትዮጵያ ዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ዙሪያ የሚያደርጉትን ትብብር ማጠናከራቸው የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው” ብለዋል።

 

የኢትዮጵያው ሚኒስትር በበኩላቸው፤ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂ ውጤቶችን እንዲሁም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትግበራን በተመለከተ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

 

“ኢትዮጵያ...በዲጂታል ትራንስፎርሜሽንና ኢኖቬሽን ዘርፍ ከአፍሪካ ወንድምና እህት ሀገራት ጋር በትብብር ለመሥራትና በጋራ ለማደግ ሙሉ ዝግጁነት አላት” ሲሉ አረጋግጠዋል።

ሁለቱ ሀገራት በቀጣይ በተመረጡ ዘርፎች በመተባበር የጋራ ተጠቀሚነትና ዕድገትን ለማጎልበት እንደተስማሙ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ያጋራው መረጃ አመልክቷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0