18 ሰዎችን ነክሳ ለያዥ ለገናዥ ያስቸገረችው ጠበኛ ጦጣ
19:05 07.08.2026 (የተሻሻለ: 19:14 07.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
18 ሰዎችን ነክሳ ለያዥ ለገናዥ ያስቸገረችው ጠበኛ ጦጣ
በእስያዊቷ ሀገር ኢንዶኔዢያ፣ ተምቢላሃን ከተማ 18 ሰዎችን የነከሰችው ይህች ጠበኛ ጦጣን፤ በቁጥጥር ስር ለማዋል ሦስት ቀናት ፈጅቷል።
የመጀመሪያው ጥቃት ከተፈጸመ በኋላ 40 ትምህርት ቤቶች በጊዜያዊነት የተዘጉ ሲሆን፤ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ደግሞ ትምህርታቸውን በኦንላይን (በርቀት) ለመከታተል ተገደዋል።
ጦጣዋ በአሁኑ ወቅት የእብድ ውሻ በሽታ ይኖርባት እንደሆነ ለማወቅ ምርመራ እየተደረገላት እንደሚገኝም ተሰምቷል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለጸገ ተንቀሳቃሽ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X