- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

ከእውቀት ተጠቃሚነት ወደ እውቀት አምራችነት፦ የአፍሪካ ትምህርት ሥርዓት የወደፊት ጉዞ

ከእውቀት ተጠቃሚነት ወደ እውቀት አምራችነት፦ የአፍሪካ ትምህርት ሥርዓት የወደፊት ጉዞ
ሰብስክራይብ

“ችግሩ የአፍሪካውያን የአእምሮ ወይም የፈጠራ አቅም ማነስ አይደለም፤ በፈጠራችን የበለፀግን ነን። ዋናው ተደቅኖብን ያለው ፈተና የትምህርትና የምርምር ሥርዓታችን ታሪክ አጋጣሚ ሆኖ ለአዲስ ፈጠራ ይልቅ ለእውቀት ማስተላለፍ ብቻ ተቀርጾ መቆየቱ ነው።” ሲሉ በርቀት ትምህርት ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት አደራጀው ምህረት (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።

በተጨማሪም “የአፍሪካ የወደፊት ተወዳዳሪነት የሚወሰነው ምን ያህል እውቀት እንመገባለን (ንባብና ትምህርት ላይ ብቻ እንደርሳለን) በሚለው ሳይሆን፤ ምን ያህል እውቀትን ውጤታማ በሆነ መንገድ እናመርታለን፣ እንተግብራለን፣ እንዲሁም ለዓለም እናካፍላለን በሚለው ላይ ነው።”ሲሉ አክለው አብራርተዋል።

በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅታችን፣ ከአደራጀው ምህረት (ዶ/ር) ጋር በመሆን አፍሪካ ለወደፊቱ ትውልድ የሚያስፈልጋትን መፍትሔ አውጪ እና ፈጠራ ታከለበት የትምህርት ፍልስፍና እንዴት መገንባት እንዳለባት በጥልቀት እንወያያለን።

ሙሉውን መረጃ ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ይከታተሉ፡

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ : Apple PodcastsSpotifyDeezerAfripodsPodcast AddictPocket CastsCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0