ከአራት ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ስለ ኢትዮጵያ እጣፈንታ – ሀገራዊ ምክክር

ሰብስክራይብ

ከአራት ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ስለ ኢትዮጵያ እጣፈንታ – ሀገራዊ ምክክር

ምክክሩ የሀገሪቱን ወደፊት አቅጣጫ ለመቅረጽ ትልቅ ተስፋ የጣለበት እንደሆነ ተሳታፊዎቹ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

"መንግሥት በሕገ መንግሥቱ ያስቀመጠውን በሃይማኖት ጉዳይ መንግሥት አይገባም፣ በመንግሥት ጉዳይም ደግሞ ሃይማኖት አይገባም የሚል ጣልቃ ገብነትን ጨምሮ [...] በሃይማኖት በኩል አለ የምንለውን ችግር መፈታት ስላለበት፣ እርስ በርሳችን በዚያ በሃይማኖት ጉዳይ ላይ እየተወያየን እንገኛለን።" ሲሉ የአማራ ክልል የሰላም ምክር ቤት ሊቀመንበር ያየህይራድ በለጠ ገልጸዋል፡፡

ሌላኛው ተሳታፊ የፌደራሊዝም ጉዳዮች ከፍተኛ ባለሙያው ዶክተር ኃይለኢየሱስ ታደሰ መድረኩ ለውይይት የሚመች እና አሳታፊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

"ሰፊ ውይይት እያደረግን ነው። ነገሮችን ያደራጁበት መንገድ በጣም ለውይይት የሚመች ነው። ሐሳቡን እንዲያወጣ፣ ሁሉም ተሳትፎ እንዲያደርግ የሚጋብዝ ነው።”

ስፑትኒክ አፍሪካ የምክክሩ ተሳታፊዎችን እስካሁኑ ሂደት ከምክክሩ ስለሚጠብቋቸው ውጤቶች እና አጠቃላይ ምልከታቸው ላይ አመጋግሯቸዋል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0