የሂሮሺማ ከንቲባ ጃፓንን በሩሲያ ጥላቻ እያደነዘዙ ነው፤ ነገር ግን ቦምቡን ማን እንደጣለው ዘንግተዋል - ዛካሮቫ

© telegram sputnik_ethiopiaየሂሮሺማ ከንቲባ ጃፓንን በሩሲያ ጥላቻ እያደነዘዙ ነው፤ ነገር ግን ቦምቡን ማን እንደጣለው ዘንግተዋል - ዛካሮቫ
የሂሮሺማ ከንቲባ ጃፓንን በሩሲያ ጥላቻ እያደነዘዙ ነው፤ ነገር ግን ቦምቡን ማን እንደጣለው ዘንግተዋል - ዛካሮቫ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 06.08.2026
ሰብስክራይብ

የሂሮሺማ ከንቲባ ጃፓንን በሩሲያ ጥላቻ እያደነዘዙ ነው፤  ነገር ግን ቦምቡን ማን እንደጣለው ዘንግተዋል - ዛካሮቫ

የአቶሚክ ቦምብ ድብደባው መታሰቢያ ቀን ላይ፣ የሂሮሺማ ከንቲባ ለከተማቸው መከራ ተጠያቂ የሆነችውን ሀገር (አሜሪካን) ዳግም ሳያነሱ ቀርተዋል። ይልቁንም አጋጣሚውን በዩክሬን ጉዳይ ሩሲያን ለማጥቃት ተጠቅመውበታል ሲሉ የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ገልፀዋል።

"የምዕራባውያን ትረካዎች የተጣመመ መስተዋት ነጸብራቁን ብቻ ሳይሆን ወደ እሱ የሚመለከቱትን ሰዎች ንቃተ-ህሊናም ያጣምማል" ሲሉ ዛካሮቫ አጽንኦት ሰጥተዋል።

ከንቲባው "ይህንን የሀሰት መፈክር ዓመት ከዓመት እየደገሙ፣ ጃፓናውያንን በሩሲያ ጥላቻ ድግምት አእምሯቸውን የሚያደነዝዙ ቢሆንም"፣ ሩሲያ የሂሮሺማ እና ናጋሳኪ ሰለባዎችን ሁልጊዜም እንደምታስታውስ እና አደጋውንም 'ተቀባይነት የሌለው ጭካኔ' አድርጋ እንደምትጠቅሰው ገልጸዋል።

"በሩቅ ምስራቅ በጃፓን ወረራ ምክንያት የተከሰተው መከራ እንዳለ ሆኖ፣ ህዝባችን የነዚያን ሁለት ከተሞች ሰለባዎች መቼም አልረሳቸውም" ሲሉ ዛካሮቫ ንግግራቸውን አጠናቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0