በኢትዮጵያ አዲስ የሞለኪዩላር ቲቢ ምርመራ ማሽኖች ይፋ ተደረጉ
17:45 06.08.2026 (የተሻሻለ: 17:54 06.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በኢትዮጵያ አዲስ የሞለኪዩላር ቲቢ ምርመራ ማሽኖች ይፋ ተደረጉ
አዲሱን ቴክኖሎጂ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር እና ከአጋር ተቋማት ጋር በመተባበር ይፋ አድርገውታል፡፡
ተንቀሳቃሽ የሆነው አዲሱ ቴክኖሎጂ፦
የቲቢ (የሳንባ ነቀርሳ) በሽታ ምርመራን የሚያሻሽሉ እና የሚያፋጥን ነው፡፡
በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያዎች፣ በማረሚያ ቤቶች፣ በማዕድን ማውጫዎች እና በአርብቶ አደር አካባቢዎች ለሚኖሩ ማኅበረሰቦች የምርመራ አገልግሎት ተደራሽነትን በእጅጉ ያሳድጋል።
በመጀመሪያው ምዕራፍ 268 የሞለኪዩላር ቲቢ ምርመራ ማሽኖች በ134 ጤና ጣቢያዎች ይገጠማል፡፡
በቀጣይ ተጨማሪ 3,000 የምርመራ ማሽኖችን በመግዛት በመላ አገሪቱ ተደራሽ ለማድረግ ዝግጅት ተጠናቋል።
ቴክኖሎጂውን በብቃት ሥራ ላይ ለማዋል ለጤና ባለሙያዎች የአሰልጣኞች ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X