ሶቪዬት ሕብረት ለአፍሪካውያን የሳይንስ ትምህርት ስትሰጥ አውሮፓ ግን የሥነ-ሰብ ትምህርቶችን ብቻ ትሰጥ ነበር - የማሊ ባለሥልጣን

ሰብስክራይብ

ሶቪዬት ሕብረት ለአፍሪካውያን የሳይንስ ትምህርት ስትሰጥ አውሮፓ ግን የሥነ-ሰብ ትምህርቶችን ብቻ ትሰጥ ነበር - የማሊ ባለሥልጣን

የሶቪዬት ዩኒቨርሲቲዎች ከአውሮፓ ተቋማት ይልቅ የበለጠ ክፍት ስለነበሩ በርካታ ታዋቂ አፍሪካውያን ሳይንቲስቶችን ለማሠልጠን ማገዛቸውን የማሊ የመከላከያ፣ የደህንነት እና የሲቪል ጥበቃ ኮሚሽን ምክትል ፕሬዝዳንት ፉሴት ኦዋታራ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

"እ.ኤ.አ. በ1960ዎቹ መጀመሪያ የአፍሪካ ሀገራት በተለይም ፈረንሳይኛ ተናጋሪ ሀገራት ነፃነታቸውን ሲያገኙ፣ ወደ ፈረንሳይ እና ሌሎች ሀገራት የሄዱት በዋናነት ሥነ-ሰብ (ሂዩማኒቲስ) ነክ ለሆኑ ትምህርቶች ብቻ ዕድል አግኝተው ነበር" ሲሉ ጠቁመዋል።

በሩሲያዋ ሮስቶቭ-ኦን-ዶን ከተማ የተማሩት ኦዋታራ አክለው እንዳሉት፣ "ሩስኪ ግላጎል" የተሰኘው ዓለም አቀፍ የሥነ-ጽሑፍ ውድድር ስኬት እንደሚያሳየው የሩሲያ ቋንቋ ዛሬ በከፍተኛ ሁኔታ እየተስፋፋ ይገኛል።

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0