የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወልደ ገብረማሪያም የኤር ኢንዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
18:25 05.08.2026 (የተሻሻለ: 18:34 05.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቀድሞው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ተወልደ ገብረማሪያም የኤር ኢንዲያ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
ኤር ኢንዲያ ኢትዮጵያዊውን ተወልደ ገብረማሪያም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ እና ማኔጂንግ ዳይሬክተር አድርጎ መሾሙን አስታውቋል።
ተወልደ በአዲሱ ኃላፊነታቸው አየር መንገዱ ያጋጠሙትን የፋይናንስ እና የአሠራር ፈታኝ ሁኔታዎች የመምራት እና የመወጣት ኃላፊነት ተሰጥቷቸዋል።
በአቬሽን ዘርፍ ሰፋ ያለ ልምድ ያካበቱት ተወልደ፣ በፍቃዳቸው ኃላፊነታቸውን የለቀቁትን የኤር ኢንዲያ የቀድሞ ኃላፊ ካምፕቤል ዊልሰንን በመተካት ከመጪው መስከረም መጨረሻ ጀምሮ ሥራቸውን ይጀምራሉ ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X