ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ ልታስተናግድ ነው
12:59 05.08.2026 (የተሻሻለ: 13:04 05.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ 76ኛውን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ኮሚቴ ጉባኤ ልታስተናግድ ነው
ኢትዮጵያ ከዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ጋር በመተባበር የምታስተናግደው ጉባዔ ከነሐሴ 18 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ይካሄዳል።
የጉባኤው ትኩረቶችና የሚጠበቁ ውሳኔዎች፦
🟠 የአኅጉሪቱን የጤና ቅድመ-አጀንዳዎች መገምገም፣
🟠 የጤና ሥርዓቶችን ማጠናከር፣
🟠 አጠቃላይ የጤና ሽፋን ተዳራሽነትን ማፋጠን፣
🟠 የድንገተኛ አደጋዎች ዝግጁነትን ማሳደግ እና
🟠 አዳዲስ የኅብረተሰብ ጤና ፈታኝ ችግሮችን መከላከል።
ከ47 የአፍሪካ አባል ሀገራት የተወጣጡ የጤና ሚኒስትሮች፣ ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የዓለም አቀፍ ድርጅቶች ተወካዮች እና ለጋሾችን ጨምሮ ከ600 በላይ ተወካዮች በጉባኤ ላይ ይሳተፋሉ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X