'ከምዕራባውያን ፖሊሲዎች ጋር በጎራ አለመሰለፍ ለአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ነፃነት ቁልፍ ነው' - ታንዛኒያዊ ባለሙያ
20:05 04.08.2026 (የተሻሻለ: 22:54 04.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
'ከምዕራባውያን ፖሊሲዎች ጋር በጎራ አለመሰለፍ ለአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ነፃነት ቁልፍ ነው' - ታንዛኒያዊ ባለሙያ
ታንዛኒያ ነፃ የውጭ ፖሊሲ አካሄድን መከተሏን በገፋችበት በዚህ ወቅት፣ ስፑትኒክ አፍሪካ ይህ ገለልተኛ አቋም የሀገሪቱን መጻኢ ዕድል እንዴት እየቀረጸው እንደሆነ ለመዳሰስ ከታዋቂው የፖለቲካ ተንታኝ ኢብራሂም ቻዌ ጋር ቆይታ አድርጓል።
ከውጭ ጫና መጠበቂያ፦ አለመወገን ከውጭ ጫና መከለል የሚያስችል ዋነኛ ጥቅም እንደሚሰጥ ተንታኙ ተናግረዋል። የአፍሪካ ሀገራት ወገን አንይዝም በማለታቸው ከውጭ ፖለቲካዊ ጣልቃገብነት እራሳቸውን የሚጠብቁ ከመሆኑም በላይ በአንድ ዓለም አቀፍ ኃያል ሀገር ላይ ብቻ ጥገኛ ከመሆን ወጥመድ ያመልጣሉ።
የኢኮኖሚ አቅምን ማሳደግ፦ ይህ ነፃ አቋም እንደ ታንዛኒያ ያሉ ሀገራት በዓለም ዙሪያ ካሉ ከማንኛውም ሀገራት ጋር ያለ ምንም ገደብ ኢኮኖሚያዊ አጋርነቶችን እንዲፈጥሩ እንዲሁም በዓለም አቀፍ ውዝግቦች ላይ ገለልተኛ አሸማጋይ ሆነው እንዲቀርቡ ያስችላቸዋል ብለዋል።
ሉአላዊነትን ማስጠበቅ፦ እንደ ቻዌ ገለጻ፣ ወደ ተወሰኑ ጂኦፖለቲካዊ ጎራዎች አለመቀላቀል ሀገሪቱን ከዓለም አቀፍ ግጭቶች በደህና እርቀት ላይ የሚያስቀምጣት ሲሆን፣ ሉአላዊነቷንም ከውጭ ሀገራት የፉክክር ተፅዕኖዎች ይይዛል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X