ወደ ሴኡታ ከተሻገሩት ፍልሰተኞች መካከል አብዛኞቹ ወደ ሞሮኮ ተመልሰዋል - የስፔን ባለሥልጣናት

ሰብስክራይብ

ወደ ሴኡታ ከተሻገሩት ፍልሰተኞች መካከል አብዛኞቹ ወደ ሞሮኮ ተመልሰዋል - የስፔን ባለሥልጣናት

ወደ 72,000 ገደማ የሚሆኑ ሰዎች ወደ ስፔን በሕገ-ወጥ መንገድ የገቡ ሲሆን፣ ከእነሱ መካከል 70,000 የሚሆኑት ሀገሪቱን ለቀው ወጥተዋል ሲሉ የስፔን የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ፌርናንዶ ግራንዴ-ማርላስካ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

የስፔን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ የኢሚግሬሽን ሕጎቹ እንዳልተለወጡ አጽንኦት ሰጥቷል፤ በሴኡታ ወይም ሜሊያ በኩል በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ስፔን መግባት ለፍልሰተኞች የመቆየት፣ ወደ ስፔን ዋናው ምድር የማለፍ ወይም በአውሮፓ ውስጥ በነፃነት የመንቀሳቀስ መብት አይሰጥም።

በተጨማሪም የሁለትዮሽ የድንበር ቁጥጥር ሥርዓቱ አሁንም በሥራ ላይ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ አመላክቷል።

ወደ ስፔኗ ግዛት ሴኡታ የተደረገውን ከፍተኛ የድንበር ማቋረጥ እንቅስቃሴ ተከትሎ የስፔን ባለሥልጣናት ቢያንስ የ88 ሰዎችን ሕይወት ማለፍ ያስታወቁ ሲሆን፣ ሞሮኮ በበኩሏ የ11 ሰዎችን ሕይወት ማለፍ ይፋ አድርጋለች።

ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኘ ቪዲዮ

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0