በሴኡታ የታየው የፍልሰት ማዕበል በማኅበራዊ ጫናዎች እና በፖለቲካዊ ውጥረቶች የተገፋ ነው - ሞሮኮአዊ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

በሴኡታ የታየው የፍልሰት ማዕበል በማኅበራዊ ጫናዎች እና በፖለቲካዊ ውጥረቶች የተገፋ ነው - ሞሮኮአዊ ባለሙያ

በዓብደልማሊክ እሳዲ ዩኒቨርሲቲ ፕሮፌሰር እና የዓለም አቀፍ የቀውስ ክትትል ማዕከል ኃላፊ ዶክተር አህመድ ዳርዳሪ ወደ ስፔኗ ግዛት ሴኡታ የተደረገው የቅርቡ የፍልሰት ማዕበል እ.ኤ.አ. በ2021 ከተከሰተው ቀውስ በላይ የሆነ እና ታይቶ የማይታወቅ የጫና ደረጃን ያሳያል ሲሉ ገልፀዋል።

ቀውሱ የመነጨው የማኅበረ-ኢኮኖሚያዊ ሁኔታዎች ቅንጅት እና ወደ አውሮፓ ለመግባት የተሳሳተ ተስፋ ከፈጠሩ በማኅበራዊ ሚዲያ ከተሰራጩ የሐሰት መረጃዎች እንደሆነ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

🟠 በሞሮኮ እና በስፔን መካከል በሴኡታ እና ሜሊያ ላይ የቀጠለው ውዝግብ ሁኔታውን የበለጠ አወሳስቦታል ሲሉ ዶክተር ዳርዳሪ አክለው ገልጸዋል።

🟠 አብዛኞቹ ፍልሰተኞች ሴኡታ መድረስ ወደ አውሮፓ ህብረት ለመሻገር ዋስትና እንደማይሆን ከተረዱ በኋላ ወደ ሞሮኮ ተመልሰዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0