የኢትዮጵያ የገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ተሞክሮ ወደ ታንዛኒያ
12:35 04.08.2026 (የተሻሻለ: 12:44 04.08.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ተሞክሮ ወደ ታንዛኒያ
የታንዛኒያ የማኅበራዊ እንቅስቃሴ ፈንድ ልዑክ በኢትዮጵያ የ5 ቀናት የደቡብ-ደቡብ የልምድ ልውውጥ ጉብኝት ጀምሯል።
የጉብኝቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
ዋና ዓላማ፦ ኢትዮጵያ በገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት መርሃግብር ያካበተቸውን ስኬታማ ተሞክሮ በታንዛኒያም በመቀመር ተግባራዊ ማድረግ።
የትኩረት መስኮች፦ በአየር ንብረት ተስማሚ የማኅበረሰብ ሥራዎች፣ የአቅም ግንባታ እና የዲጂታል አሰራሮች ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ተካሂደዋል።
የመስክ ምልከታ፦ በድሬዳዋ የሚገኙ የሶሻል ሴፍትኔት፣ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ እና የዲጂታል መሣሪያዎች አጠቃቀም ሥራዎችን በአካል ይጎበኛሉ።
ይህ የልምድ ልውውጥ መድረክ በኢትዮጵያ ግብርና ሚኒስቴር፣ በታንዛኒያ ልዑካን ቡድን፣ በዓለም ባንክ እና በዓለም ምግብ ፕሮግራም አዘጋጅነት እየተካሂደ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X