በሱዳን ሰሜን ዳርፉር ፍርድ ቤት ላይ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃት የጎሳ መሪዎችን ጨምሮ ቢያንስ 37 ሰዎች ተገደሉ

© telegram sputnik_ethiopiaበሱዳን ሰሜን ዳርፉር ፍርድ ቤት ላይ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃት የጎሳ መሪዎችን ጨምሮ ቢያንስ 37 ሰዎች ተገደሉ
በሱዳን ሰሜን ዳርፉር ፍርድ ቤት ላይ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃት የጎሳ መሪዎችን ጨምሮ ቢያንስ 37 ሰዎች ተገደሉ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.08.2026
ሰብስክራይብ

በሱዳን ሰሜን ዳርፉር ፍርድ ቤት ላይ በተሰነዘረ የድሮን ጥቃት የጎሳ መሪዎችን ጨምሮ ቢያንስ 37 ሰዎች ተገደሉ

በካብካቢያ ጉራ-ዛዊያ ወረዳ በሚገኘው ፍርድ ቤት የሀገር ሽማግሌዎች እና የጎሳ መሪዎች ስብሰባ ወቅት በተሰነዘረው ጥቃት 37 ሰዎች ሲገደሉ 40 ያህሉ ደግሞ መቁሰላቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል።

ጥቃቱን የተመለከቱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

🟠 በጉራ-ዛዊያ ወረዳ የጥቃቱ ዒላማ የሆነው ስብሰባ የሱዳን ጦርን የኮርዶፋን ግስጋሴ ተከትሎ የፈጥኖ ደራሹ ኃይል ያቀረበውን የቅስቀሳ ጥሪ ውድቅ ያደረጉ የሀገር ሽማግሌዎችን ብቻ የተገኙበት እንደነበር የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

🟠 በሌላ በኩል የአማፂው ፓራሚሊተሪ ቡድን የፖለቲካ ክንፍ የሆነው የ "ታሲስ" ጥምረት ጥቃቱን ያደረሰው የመንግሥት ኃይል ነው ብሏል። የሱዳን ጦር ግን እስካሁን ለዚህ ክስ ምላሽ አልሰጠም።

🟠 ጥቃቱ፤ ካርቱምን ከሰሜን ኮርዶፋን ጋር የሚያገናኘው ቁልፍ የወጪ ንግድ መንገድ ነፃ መውጣቱን ጨምሮ፤ የሱዳን ጦር በምዕራባዊ አካባቢዎች ያስመዘገበውን ስትራቴጂካዊ የበላይነት ተከትሎ የመጣ ነው።

🟠 የሱዳን ጦር የአማፂ ቡድኑን አቅም ለማዳከም በዳርፉር በሚገኙ የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ይዞታዎች ላይ የሚያደርገውን የድሮን ጥቃት አጠናክሮ ቀጥሏል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0