የአፍሪካ የማዕድን ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት መነቃቃት እያሳየ ነው ተባለ

© telegram sputnik_ethiopiaየአፍሪካ የማዕድን ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት መነቃቃት እያሳየ ነው ተባለ
የአፍሪካ የማዕድን ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት መነቃቃት እያሳየ ነው ተባለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 03.08.2026
ሰብስክራይብ

የአፍሪካ የማዕድን ኢንዱስትሪ የኢንቨስትመንት መነቃቃት እያሳየ ነው ተባለ

​ለሰው ሰራሽ አስተውሎት መሠረተ ልማት ወሳኝ ማዕድን የሆነውን የዓለማችንን የመዳብ ምርት 20% ገደማ የምትሸፍነዋ አኅጉሪቱ፤ በማዕድን ኢንዱስትሪዋ ላይ ከፍተኛ የኢንቨስትመንት ፍሰት እያስተናገደች ትገኛለች።

​ከአፍሪካ ማይኒንግ ዊክ ምንጮች በተገኘው መረጃ መሠረት፤ ዓለም አቀፍ የመዳብ ፍላጎት በዓመት ወደ 50 ሚሊዮን ቶን ያድጋል ተብሎ መጠበቁ፤ ለዋና ዋና የአፍሪካ የመዳብ አምራቾች የበርካታ ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ዕድል ይፈጥርላቸዋል።

​ በኮንጎ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ  የሚገኘው የካሞአ-ካኩላ የመዳብ ኮምፕሌክስ፤ ከ 8 ቢሊዮን ዶላር በላይ ኢንቨስትመንት የሳበ ሲሆን በአሁን ወቅት በዓመት ወደ 520,000 ቶን የሚጠጋ መዳብ እያመረተ ይገኛል።

​ ዛምቢያ ለሚንጎምባ የመዳብ ፕሮጀክት 2.2 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት አግኝታለች። ፕሮጀክቱ በ2031 ማምረት ሲጀምር በዓመት እስከ 300,000 ቶን ምርት ይሰጣል።

​ ቦትስዋና ለኮማካው የመዳብ ማዕድን ማውጫ 1.85 ቢሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት ያገኘች ሲሆን ከማስፋፊያ ሥራው በኋላ በዓመት 130,000 ቶን መዳብ ያመርታል ተብሎ ይጠበቃል።

​ በልማት ደረጃ ላይ እያለ 1 ቢሊዮን ዶላር ገደማ መሳብ የቻለው የናሚቢያው ሃይብ የመዳብ ፕሮጀክት፤ የሀገሪቱ ቀዳሚ የመዳብ ማዕድን ማውጫ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል። የማምረት አቅሙም በዓመት ከ90,000 እስከ 95,000 ቶን መዳብ እንደሚሆን ይገመታል።

​ይህ ኢንቨስትመንት የሥራ ዕድልን በመፍጠር፣ የኢኮኖሚ ዘርፎችን በማስፋት እና የአካባቢ መሠረተ ልማቶችን በማሳደግ የአፍሪካ ሀገራትን በእጅጉ ይጠቅማል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0