የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቁመና አደገኛውን የመካከለኛው ምሥራቅ የባሕር መተላለፊያ ማለፍ እንዳስቻለ ተነገረ

© telegram sputnik_ethiopiaየኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቁመና አደገኛውን የመካከለኛው ምሥራቅ የባሕር መተላለፊያ ማለፍ እንዳስቻለ ተነገረ
የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቁመና አደገኛውን የመካከለኛው ምሥራቅ የባሕር መተላለፊያ ማለፍ እንዳስቻለ ተነገረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.08.2026
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ዲፕሎማሲ ቁመና አደገኛውን የመካከለኛው ምሥራቅ የባሕር መተላለፊያ ማለፍ እንዳስቻለ ተነገረ

 

የኢትዮጵያ የባሕር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ከተለዋዋጩ የቀይ ባሕር እና ሰፊው የመካከለኛው ምሥራቅ የፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ መርከቦቹ ላይ መስተጓጎል እንዳይደርስ አማራጮችን እያሰሰ ነው።

ድርጅቱ እንደ ሁኔታው በቀጣናው አነስተኛ መጋቢ መርከቦችን ስለማሰማራት ወይም መርከቦችን ረዘም ባለ ርቀት አቅጣጫ በመቀየር ስለማጓጓዝ እየገመገመ ይገኛል።

የኢባትሎ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አብዱልበር ሸምሱ፤ "ሁኔታው አሁንም ተለዋዋጭ እና በሂደት ላይ ያለ ስለሆነ፤ ውሳኔያችንን በንግድ ትንታኔ ላይ ተመስርተን እናሳልፋለን" ሲሉ ለሀገር ውስጥ የግል ሚዲያ ተናግረዋል።

ኃላፊው አክለውም፤ ሀገሪቱ የዲፕሎማሲ አቅሟን ተጠቅማ የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ የሚያውለበልቡ መርከቦች አደገኛና ተለዋዋጭ በሆኑ የውሃ አካባቢዎች ውስጥ ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ማስቻሏን አንስተዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0