ሩሲያ እና ሞሪታንያ በኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

© telegram sputnik_ethiopiaሩሲያ እና ሞሪታንያ በኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ
ሩሲያ እና ሞሪታንያ በኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 01.08.2026
ሰብስክራይብ

ሩሲያ እና ሞሪታንያ በኢኮኖሚ ትብብር ዙሪያ የመግባቢያ ስምምነት ተፈራረሙ

​ የሩሲያ የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትር ማክሲም ሬሼትኒኮቭ እና የሞሪታንያ የኢኮኖሚ እና ልማት ሚኒስትር አብደላሂ ሼክ ሲዲያ፤ በበይነ-መረብ በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት የመግባቢያ ስምምነቱን መፈራረማቸውን የሞሪታንያ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

​ የስምምነቱ ትኩረት የሁለቱ ወገኖች የጋራ ፍላጎት በሆኑት የዓሣ ሀብት፣ ሥነ-ምድር፣ የመሬት ውስጥ ሀብት አጠቃቀም እና በሌሎች ዘርፎች በሚከናወኑ ፕሮጀክቶች ላይ እንደሚሆን ሼክ ሲዲያን የጠቅሰው ዘገባ አመልክቷል።

 

​"ግብርና፣ የሥነ-ምድር ፍለጋ፣ የማዕድን ማውጣት፣ የኤሌክትሪክ ኃይል እና የዓሣ ሀብት በሁለትዮሽ ትብብራችን ውስጥ ተስፋ ሰጪ መስኮች ናቸው" ሲሉ ሬሼትኒኮቭ ተናግረዋል።

​ሁለቱ ወገኖች በዓሣ ሀብት ዘርፍ ያላቸው ትብብር ከ50 ዓመታት በላይ የዘለቀና የቆየ የጋራ አጋርነት እንደሆነም ተነስቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0