ማይናማር ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ሂደት ልምድ ለመቅሰም ልዑካኗን እንደምትልክ አስታወቀች
14:19 01.08.2026 (የተሻሻለ: 14:24 01.08.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ማይናማር ከኢትዮጵያ ሀገራዊ የምክክር ሂደት ልምድ ለመቅሰም ልዑካኗን እንደምትልክ አስታወቀች
የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ሚን ኡንግ ላይንግ በጃፓን በማይናማርና በላኦስ የኢትዮጵያ አምባሳደር ዳባ ደበሌ ጋር ባደረጉት ውይይት፤ ኢትዮጵያ ለአለመግባባቶችና ግጭቶች ምክንያት የሆኑ ጉዳዮችን አንጥሮ ለማውጣት እያካሄደች የምትገኘውን ብሔራዊ ምክክር አድንቀዋል።
ከብሔራዊ ምክክሩ ልምድ ለመቅሰም ራሱን የቻለ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ ለመላክ እንደሚፈልጉ መግለጻቸውንም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በሌላ በኩል በሕገ-ወጥ አዘዋዋሪዎች በማጎሪያዎች እንዲገቡ የተደረጉ ኢትዮጵያውያንን ከተደራጁ የወንጀል ቡድኖች ለማስጣል መንግሥታቸው የሚቻለውን ሁሉ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል፡፡
አምባሳደሩ በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይገኙ የነበሩ 1,308 ኢትዮጵያውያን ከዚህ ቀደም ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ለተደረገው ድጋፍ ምሥጋናም አቅርበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X