ታንዛኒያ በመረጃ ጥገኝነት ሳቢያ በሚመጣ “ዲጂታል ኒዮ-ኮሎኒያሊዝም” ዙሪያ አስጠነቀቀች
17:40 31.07.2026 (የተሻሻለ: 17:44 31.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ታንዛኒያ በመረጃ ጥገኝነት ሳቢያ በሚመጣ “ዲጂታል ኒዮ-ኮሎኒያሊዝም” ዙሪያ አስጠነቀቀች
በዶዶማ በተካሄደው 3ኛው የዶዶማ ዩኒቨርስቲ የሳይንስ እና ጤና ጉባኤ ላይ በጤና ሚኒስቴር የምክትል ዋና ጸሐፊ ኤማኑኤል ታያሪ፤ የጤናው ዘርፍ ዕድገት ከእንግዲህ ከኤአይ ቴክኖሎጂዎች ተለይቶ ሊታይ እንደማይችል ተናግረዋል።
“የራሳችንን ዕውቀት ፈጥረን ካላሳተምን፤ የታንዛኒያን ነባራዊ ሁኔታ በማያንጸባርቅ መረጃ ላይ በተገነቡ የኤአይ ሥርዓቶች ላይ ጥገኛ መሆናችንን እንቀጥላለን። ይህም ከእኛ ሁኔታ ጋር የማይጣጣሙ ምላሾችን ያስከትላል” ማለታቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ይህም በርካታ የኤአይ ሥርዓቶች ከታንዛኒያ ነባራዊ ሁኔታ ይልቅ በአውሮፓ እና በአሜሪካ ከተመረቱ መረጃዎች አብልጠው እንዲማሩ ያደርጋቸዋል ሲሉ አክለዋል።
በሀገር ውስጥ የሚከማቹ የጤና መረጃዎችን መጠበቅ አስፈላጊ መሆኑን ያሰመሩበት ታያሪ፤ በጤናው ዘርፍ ጥቅም ላይ የሚውሉ ሁሉም የኤአይ ሥርዓቶች ሥራ ላይ ከመዋላቸው በፊት በሚመለከታቸው አካላት መጽደቅ እንዳለባቸው እና እንደነዚህ ያሉ ቴክኖሎጂዎችን በሀገር ውስጥ የማልማት አቅምን ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X