ሩሲያ ኃይሎች ባለፈው ሳምንት 12 ሰፈራዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋላቸውን የመከላከያ ሚኒስትር አስታወቀ
13:49 31.07.2026 (የተሻሻለ: 13:54 31.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሩሲያ ኃይሎች ባለፈው ሳምንት 12 ሰፈራዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋላቸውን የመከላከያ ሚኒስትር አስታወቀ
ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ ተጨማሪ አካባቢዎች ነፃ መውጣታቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል፦
▪ በካሃርኮቭ ክልል ቬሮቭካ፣
▪ በዶኔትስክ ሕዝባዊ ሪፐብሊክ ስቴንኪ ነፃ ከወጡት መካከል ይገኙበታል።
በተመሳሳይ ሩሲያ በዩክሬን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ 15 የተቀናጁ ጥቃቶችን እና አንድ ከፍተኛ ድብደባ መፈጸሟንም ሚኒስቴሩ ጨምሮ አስታውቋል።
የሩሲያ ጦር እ.ኤ.አ 2026 ከገባ በኋላ በልዩ ወታደራዊ ዘመቻ ቀጣናዎች ሙሉ ግስጋሴውን በመቀጠል፤ በዶንባስ እና ባሻገር አካባቢዎችን በተከታታይ ነፃ በማውጣት እንዲሁም በድንበር አካባቢዎች ያለውን የደህንነት ከለላ ቀጣና እያሰፋ ይገኛል።
ቪዲዮዉ ቬሮቭካ ነፃ ስትወጣ ያሳያል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X