- Sputnik አፍሪካ, 1920
Drum of Changes
ከጥንታዊ የስልጣኔ ምድሮች እስከ ዘመናዊ ከተሞች ልብ፣ በአፍሪካ አዲስ ጥሪ እየተስተጋባ ይገኛል። አፍሪካ የዓለምን የወደፊት ሁኔታ የምትቀርጽ ቸል ልትባል የማይገባት ኃይል ሆና እያደገች ነው። ለአስርት ዓመታት አፍሪካ የምትናገር፣ ነገር ግን የማትደመጥ ሆና ቆይታለች። ዛሬ ግን ጥሪው ግልፅ ነው። አፍሪካ ከዓለም የኃይል ማዕድ የሚገባትን ትክክለኛ ቦታ ትጠይቃለች። ይህ ፕሮግራምም ከአፍሪካ የሚስተጋቡ የለውጥ ድምፆችን በልካቸው ወደ አድማጭ ተመልካቾቹ ያደርሳል።

ቻድ ከአይ.ሲ.ሲ ለመውጣት ያሳለፈችው ውሳኔ፡- የምዕራቡ ዓለም መሣሪያ ለሆነው ተቋም የአፍሪካ ምላሽ?

ቻድ ከአይ.ሲ.ሲ ለመውጣት ያሳለፈችው ውሳኔ፡ የምዕራቡ ዓለም መሣሪያ ለሆነው ተቋም የአፍሪካ ምላሽ?
ሰብስክራይብ
"የምዕራቡ ዓለም የዓለም አቀፉን የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) የራሱን ፍላጎት ማስፈፀሚያ ያደረገው ይመስላል [...] ቻድ ከ አይ.ሲ.ሲ ለመውጣት ያሳለፈችው ውሳኔም ለቀሪው የአፍሪካ አህጉር ግልጽ መልዕክት አስተላልፏል 'አፍሪካ የራሷን ዕድል በራሷ የመወሰን እና የራሷን የፍትህ መንገድ የመቀየስ ጊዜዋ አሁን ነው' የሚል" ሲሉ የሕግ ባለሞያው መታገስ ዉለታው ለስፑትክ አፍሪካ ተናግረዋል።
በዛሬው የድረም ኦቭ ቼንጅስ ቀዳሚ ዝግጅታችን ቻድ ከዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) ለመውጣት የወሰደችውን ርምጃ መነሻ አድርገን የተቋሙን መዋቅራዊ አድልዎ እና በአፍሪካ የሀገርበቀል የፍትህ ስርዓቶችን የመገንባት ጥረቶችን በጥልቀት እንፈትሻለን። ለዚህም በወራቤ ዩኒቨርሲቲ የሕግ ትምህርት ቤት መምህር እና የዓለም አቀፍ ሕግ ባለሞያ መታገስ ዉለታው ጋር ተወያይተናል።
በሁለተኛው ጉዳያችን ደግሞ፣ እ.ኤ.አ ከሐምሌ 29 እስከ 30፣ 2026 በአዲስ አበባ የተካሄደውን ወርልድ ፐብሊክ ፎረም መነሻ አድርገን፤ የግብርና ዘርፉን ወደ 21ኛው ክፍለ ዘመን በማሸጋገር ረገድ የዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ሚና እንቃለን። ይህንን ጉዳይ የበለጠ እንዲያብራሩልን ከሩሲያው "ግራሚዮን ፕላስ" ኩባንያ ተወካይ ፓቬል ኮኖቭ ኒኪታ ጋር ተወያይተናል።
ሙሉ መረጃውን ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

ፖድካስታችንን በሌሎች አማራጮች ያድምጡ: Apple PodcastsDeezerSpotifyAfripods Pocket CastsPodcast AddictCastBox
አዳዲስ ዜናዎች
0