የምዕራብ አፍሪካ ሀገራትን ከፍተኛ የወርቅ ማዕድን ምርት ተከትሎ የዓለም የወርቅ ፍላጎት በታሪክ ከፍተኛ ወደሆነ 380 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ - የዓለም የወርቅ ምክር ቤት
18:39 30.07.2026 (የተሻሻለ: 18:44 30.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የምዕራብ አፍሪካ ሀገራትን ከፍተኛ የወርቅ ማዕድን ምርት ተከትሎ የዓለም የወርቅ ፍላጎት በታሪክ ከፍተኛ ወደሆነ 380 ቢሊዮን ዶላር ደረሰ - የዓለም የወርቅ ምክር ቤት
⬆ቁጥሮቹን በጨረፍታ
የ2026 የ2ኛው ሩብ ዓመት ፍላጎት፦ በ1,269 ቶን ደረጃ ላይ ጸንቶ ቀጥሏል።
የመጀመሪያው መንፈቅ ዓመት (2026) ድምር፦ 2,522 ቶን የደረሰ ሲሆን ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ+2% እድገት አሳይቷል።
የ2ኛው ሩብ ዓመት የማዕድን ምርት፦ ከቀደመው ሩብ ዓመት ጋር ሲነጻጸር +7% በመጨመር፤ እ.ኤ.አ በ2025 ተመዝግቦ የነበረውን የ948 ቶን የሁልጊዜም ከፍተኛ መጠን በልጦ ተመዝግቧል።
በምርት እድገቱ ግንባር ቀደም የሆኑት እነማን ናቸው? ሁለት ዋና ዋና የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት በወርቅ ማዕድን ምርት ላይ አስደናቂ የዓመት-ከዓመት እድገት አስመዝግበዋል፦
ቡርኪና ፋሶ፦ +17%
ጋና፦ +8%
በተቃራኒው የምርት ቅናሽ የታየባቸው ሀገራት፦
ኒካራጓ፦ (-33%)
ሜክሲኮ፦ (-23%)
አሜሪካ፦ (-12%)
ቻይና፦ (-8%)
ማዕከላዊ ባንኮች በመጀመሪያው ሩብ ዓመት ከተመዘገበው መቀዛቀዝ በኋላ በከፍተኛ ሁኔታ በማንሰራራት ከፍተኛ መጠን ያለው ግዥ (289 ቶን) ፈጽመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X