ኢትዮጵያ እና ቻይና በኢንዱስትሪ እና ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ የሁለትዮች ፎረም አካሄዱ

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ እና ቻይና በኢንዱስትሪ እና ማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ያላቸውን ትብብር ለማጠናከር ያለመ የሁለትዮች ፎረም አካሄዱ

ሀገራቱ በማኑፋክቸሪንግ፣ በብረት ምርት እና በኢንዱስትሪ አውቶማቲክ አሠራር ላይ ትኩረት በማድረግ ኢኮኖሚያዊ አጋርነታቸውን እያጠናከሩ እንደሚገኙ በመድረኩ መገለጹን የስፑትኒክ አፍሪካ ባልደረባ ዘግባለች።

በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምስራቅ እስያ ጉዳዮች ዳይሬክተር ዶ/ር አሳዬ ዓለማየሁ፣ የኢኮኖሚ እድገትን የሀገሪቱ የሉዓላዊነት አካል አድርገው በማንሳት ከቻይናውያን አጋሮች ጋር በመሆን "ድህነትን ታሪክ ለማድረግ" እንደሚሠራ ገልጸዋል።

በቻይና ንግድ ሚኒስቴር ሥር የሚገኝ ብሔራዊ ማኅበር ተወካይ ፕሮፌሰር ዣንግ፣ ከቻይና 70 ሚሊዮን አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ወደ ኢትዮጵያ የሚደረግ የቴክኖሎጂ ሽግግር እና የኢንቨስትመንት አቅም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

ቅድሚያ የሚሰጣቸው ተግባራት፦

ወደፊት በሚደረጉ ትብብሮች ለኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ማሽነሪዎችን ማቅረብ፣

ዘመናዊ የፋብሪካ አውቶሜሽን አሠራሮችን መተግበር እና

የኢትዮጵያን የተለያዩ ዘርፎች ከቻይና የቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ጋር በቀጥታ ማገናኘት፡፡

በስፑትኒክ አፍሪካ ጋዜጠኛ የተቀረጸ ቪዲዮ

 ስፑትኒክ ኢትዮጵያ |  መተግበሪያ |  X

አዳዲስ ዜናዎች
0