የኩዌቱ ጃዚራ ኤርዌይስ ወደ አዲስ አበባ የቀጥታ በረራ አገልግሎት ሊጀምር ነው
17:19 29.07.2026 (የተሻሻለ: 17:24 29.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የኩዌቱ ጃዚራ ኤርዌይስ ወደ አዲስ አበባ የቀጥታ በረራ አገልግሎት ሊጀምር ነው
አየር መንገዱ ከፊታችን ጳጉሜ 2 ቀን 2018 ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ መዲና አዲስ አበባ በሳምንት ሦስት ቀናት ቀጥታ የንግድ በረራ አገልግሎት ለመጀመር ማቀዱን አስታውቋል።
የበረራው መጀመር የሚከተሉት ጥቅሞች እንደሚኖሩት ተገልጿል፦
ለተጓዦች ተጨማሪ እና ምቹ የበረራ አማራጭ ይፈጥራል።
የቱሪዝም፣ የባህል እና የቡና ሀብት ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ለማስተዋወቅ ያግዛል፡፡
የሀገራቱን የንግድ፣ የኢንቨስትመንት እና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ያሳድጋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X