በኬንያ የተገኙ የ1.43 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ የእግር አሻራዎች ስለ ሰው ልጅ ቀደምት አባቶች ተክለ-ቁመና እና ባህሪ ገለጡ - ጥናት

© telegram sputnik_ethiopiaበኬንያ የተገኙ የ1
በኬንያ የተገኙ የ1 - Sputnik አፍሪካ, 1920, 29.07.2026
ሰብስክራይብ

በኬንያ የተገኙ የ1.43 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ የእግር አሻራዎች ስለ ሰው ልጅ ቀደምት አባቶች ተክለ-ቁመና እና ባህሪ ገለጡ - ጥናት

በሰሜን ኬንያ የሚገኘው የኮቢ ፎራ የመሬት ስብስብ የሁለቱን የ"ሆሚኒን" (የቀደምት ሰው) ዝርያዎች "ሆሞ" እና "ፓራንትሮፐስ"ን ቅሪተ አካላት ጠብቆ ማቆየቱን ተመራማሪዎች በጥናታቸው ይፋ አድርገዋል።

"የአሻራዎቹ ሥነ-ምህዳራዊ ሁኔታ እንደሚያመላክተው "ሆሚኒኖች" በዴልታ ሐይቅ ዳርቻ መኖሪያ አካባቢዎች የሚገኙ ሀብቶችን ይጠቀሙ ነበር።"

የተገኙት የእግር አሻራዎች "ስለ ቀደሙት የፕሊስቶሲን ሆሚኒኖች የሰውነት አወቃቀር፣ የሰውነት መጠን፣ የእንቅስቃሴ ሁኔታ፣ ባህሪ እና የመኖሪያ አካባቢዎች" ጠቃሚ መረጃ የሚሰጡ መሆናቸውን ተመራማሪዎች አፅንዖት ሰጥተዋል።

"የአሻራ ባለቤቶቹ ትልቅ የሰውነት መጠን ይህ የሆሚኒን ቡድን በርካታ አዋቂ ወንዶችን ያካተተ እንደነበር የሚጠቁመውን መላ ምት የሚደግፍ ሲሆን፤ ይህም የነበራቸውን ማኅበራዊ ባህሪ የሚያሳይ ቀደም ሲል ያልታየ የቀጥታ ማስረጃን ያቀርባል።"

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0