በ2026 የመጀመሪያ አጋማሽ ሩሲያ ወደ አፍሪካ የምትልካቸው የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ በ40% አደገ - አግሮኤክስፖርት

ሰብስክራይብ

በ2026 የመጀመሪያ አጋማሽ ሩሲያ ወደ አፍሪካ የምትልካቸው የግብርና ምርቶች የወጪ ንግድ በ40% አደገ - አግሮኤክስፖርት

ሩሲያ ወደ አኅጉሪቱ በግምት 2.9 ቢሊዮን ዶላር የሚያወጡ ከ11 ሚሊዮን ቶን በላይ የግብርና ምርቶችን ማቅረቧን የሩሲያ የግብርና ኤክስፖርት ልማት ማዕከል (አግሮኤክስፖርት) አስታውቋል።

በመጠን ከፍተኛ የሆኑ የወጪ ንግድ ምርቶች

ስንዴ፦ ~10.2 ሚሊዮን ቶን

ገብስ፦ ~234,000 ቶን

የአኩሪአተር ዘይት፦ ከ158,000 ቶን በላይ

የሱፍ ዘር ተረፈ-ምርት እና ዱቄት መኖ፦ ከ95,000 ቶን በላይ

የስኳር ቢት (ባቄላ) ተረፈ-ምርት ፦ ከ64,000 ቶን በላይ

ዋና ዋና ሸማቾች፦

ግብፅ 4.9 ሚሊዮን ቶን በመግዛት እና ከአጠቃላይ መጠኑ 44% ድርሻ በመያዝ በግንባር ቀደምትነት ትጠቀሳለች፡፡

ሱዳን የ11% ድርሻ በመያዝ በሁለተኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡

ኬንያ የ10% ድርሻ በመያዝ ሦስተኛዋ ግዙፍ ገዢ ነች።

በጠቅላላው ሩሲያ በ2026 የግብርና ምርቶችን ከ40 በላይ ለሚሆኑ የአፍሪካ ሀገራት መላኳን አግሮኤክስፖርት አመላክቷል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0