ሱዳን በጦርነት የወደመውን የጤና ሥርዓቷን መልሶ ለመገንባት 293 ሚሊዮን ዶላር አገኘች - ዘገባ

ሰብስክራይብ

ሱዳን በጦርነት የወደመውን የጤና ሥርዓቷን መልሶ ለመገንባት 293 ሚሊዮን ዶላር አገኘች - ዘገባ

በሀገሪቱ ከሚገኙ ሆስፒታሎች እና የመጀመሪያ ደረጃ የጤና ተቋማት ውስጥ ወደ 75 በመቶ የሚሆኑት ከደረሰባቸው ሰፊ የጦርነት ውድመት በኋላ እንደገና ሥራ መጀመራቸውን የመገናኛ ብዙኃን የጤና ሚኒስትሩን ኃይተም ሙሐመድ ኢብራሂምን ጠቅሰው ዘግበዋል።

የመልሶ ማቋቋም ዕቅዱ፦

ሚኒስቴሩ ከአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ አሰጣጥ ወደ ሥርዓታዊ የመልሶ ግንባታ ምዕራፍ እየተሸጋገረ ይገኛል።

በመጪው ረቡዕ፣ ሀገር አቀፍ የጤና አገልግሎቶችን እንደገና ለማስጀመር በዓለም ጤና ድርጅት የሚደገፈውን "የተስፋ ስትራቴጂ" ይፋ ያደርጋል።

የተገኘው የገንዘብ ድጋፍ፦

ከአካባቢው አጋሮች ጋር የተደረጉ ስምምነቶች ለመልሶ ማቋቋም ጥረቱ 293 ሚሊዮን ዶላር ያስገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ይህም ከአፍሪካ ልማት ባንክ የተገኘውን 70 ሚሊዮን ዶላር ያካትታል።

የዩኒሴፍ ቪዲዮ በሱዳን ደቡብ ኮርዶፋን የሚገኘውንና ለሕፃናት አስፈላጊ የጤና እና የሥርዓተ-ምግብ አገልግሎት የሚሰጠውን ማዕከል ያሳያል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0