የሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ "ሆሳስ" የእርሻ መንደሮች በዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ተመዘገቡ

ሰብስክራይብ

የሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ "ሆሳስ" የእርሻ መንደሮች በዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ተመዘገቡ

በደቡብ ኮሪያ ቡሳን በተካሄደው 48ኛው የዩኔስኮ የዓለም ቅርሶች ኮሚቴ ስብሰባ ላይ ይፋ ከተደረጉት አዳዲስ አስር የተመዘገቡ ቅርሶች መካከል በሳኦ ቶሜ እና ፕሪንሲፔ ደሴቶች የሚገኙ ስድስት የፖርቱጋል የቅኝ ግዛት የእርሻ መንደሮች (ሆሳስ) ይገኙበታል፡፡

▪ ሞንቴ ካፌ፣

▪ አጉዋ ኢዜ፣

▪ ዲዮጎ ቫዝ፣

▪ ሳኦ ጆአኦ፣

▪ ሰንዲ እና

▪ ቤሎ ሞንቴ።

እነዚህ ቦታዎች በጋራ የታቀደ የቅኝ ግዛት እርሻ ሥርዓትን የሚያንጸባርቁ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ያካተቱ ናቸው፡፡

▪ የቡና እና የኮኮዋ እርሻዎች፣

▪ የግብርና መሬት፣

▪ የኢንዱስትሪ መሠረተ ልማት፣

▪ የመኖሪያ አካባቢዎች እና

▪ በጥንቃቄ በተዋቀሩ የቦታ አቀማመጦች የተደራጁ የማኅበራዊ አገልግሎት ተቋማት።

ቅርሱ ከ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ ድረስ በአስገዳጅ ፍልሰት እና በግዳጅ ጉልበት ላይ የተመሠረተውን ሰፊ የቅኝ ግዛት የግብርና-ኢንዱስትሪ ሥርዓት የሚመሰክር ሲሆን፤ ባርነት ከተሻረ በኋላም ቢሆን የዓለምን የቡና እና የኮኮዋ አቅርቦት እንዲቀጥል አድርጓል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0