የአውሮፓ ቴክኖክራሲዎች የሩሲያን ባሕል "ማጥፋት ይፈልጋሉ" - የጄኔራል ደ ጎል የልጅ ልጅ

ሰብስክራይብ

የአውሮፓ ቴክኖክራሲዎች የሩሲያን ባሕል "ማጥፋት ይፈልጋሉ" - የጄኔራል ደ ጎል የልጅ ልጅ

እነዚህ ቴክኖክራሲዎች "ታሪክን እንደገና ለመጻፍ" እና የቀደሙ አባቶችን ውርስ ለማጥፋት የሚሹ ሲሆን፣ በምትኩ ከ"ግለኝነት እና የራስ-ወዳድነት ትምክህት ባሕል" በስተቀር የሚያቀርቡት ነገር የለም ሲሉ የዓለም አቀፉ የሊዮ ቶልስቶይ የሰላም ሽልማት ዳኞች ምክትል ሰብሳቢ ፒየር ደ ጎል ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

በተጨማሪም "ታሪክን ከመዘንጋት" እና በዩክሬን የናዚዝም እንደገና ማንሰራራት አስመልክቶም አስጠንቅቀዋል፡፡

"ጥንቃቄ ካላደረግን፣ ለናዚዝም መፈጠር ምክንያት የሆኑት ሁኔታዎች በሚያሳዝን ሁኔታ በዩክሬን እንደገና ያንሰራራሉ ብዬ አምናለሁ። በቬርማኽት የጦር ልብስ (መለዮ) ለብሰው የተዋጉትን የዩክሬን ናዚዎችን ስም እና ገጽታ ለማደስ የሚደረገውን ጥረት እቃወማለሁ" ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0