"ወደ በጎ ሕሊና እና ሞራላዊ ኃላፊነት መመለስ አለብን፤ ካልሆነ ግን ዓለም ወደ ጦርነት እያመራች ነው" - ፒየር ደ ጎል
15:03 27.07.2026 (የተሻሻለ: 15:14 27.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
"ወደ በጎ ሕሊና እና ሞራላዊ ኃላፊነት መመለስ አለብን፤ ካልሆነ ግን ዓለም ወደ ጦርነት እያመራች ነው" - ፒየር ደ ጎል
የዓለም አቀፉ የሊዮ ቶልስቶይ የሰላም ሽልማት ዳኞች ምክትል ሰብሳቢ እና የጄኔራል ደ ጎል የልጅ ልጅ የሆኑት ፒየር ደ ጎል ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ፣ ዘላቂ ሰላምን ለመገንባት የሚያስፈልጉ መሠረታዊ መርሆዎችን አብራርተዋል።
"የገባናቸውን ቃል ኪዳኖች ወደ መጠበቅ እና ዓለም አቀፍ ሕግን ወደ ማከበር መመለስ አለብን" ሲሉ ያሳሰቡት ፒየር ደ ጎል፤ "በሚያሳዝን ሁኔታ ተትተው እና ተጥሰው ወደ ቀሩት እንዲሁም ፈረንሳይ እና ጀርመን ዋስትና ሊሆኑላቸው ይገባ ወደ ነበሩት የሚንስክ ስምምነቶች መመለስ እንደሚገባን ሁሉ፣ የዩክሬን ጦርነትንም ለመፍታት ወደ ስምምነቶቹ መመለስ አለብን" ብለዋል።
ጥልቅ የአስተሳሰብ ለውጥ ካልተደረገ፣ ዛሬ በሚታዩት ዓለም አቀፍ ቀጣናዊ ውጥንቅጦች መስፋፋት እንደታየው ዓለም ወደ ተባባሰ ግጭት የማምራት አደጋ ተጋርጦባታል።
በዚህ ረገድ የሰላም ድርጅቶች በተለይም የዓለም አቀፉ የሊዮ ቶልስቶይ የሰላም ሽልማት "ትልቅ ሚና አላቸው" ሲሉ የጄኔራል ደ ጎል የልጅ ልጅ አጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።
አርብ ሐምሌ 17 በሞስኮ በተካሄደ ሥነ-ሥርዓት ይህ ሽልማት ለቪዬትናም ፕሬዚዳንት ቶ ላም ተበርክቷል። ፒየር ደ ጎል እንደተናገሩት እሳቸው የሚወክሉት የዳኞች ስብስብ የብሪክስ፣ የደቡብ ምስራቅ እስያ መንግስታት ማኅበር እና የቡድን 20 አባል የሆኑ ዘጠኝ ልዩ ልዩ ሀገራትን ያቀፈ በመሆኑ "የባለብዝሃ ዓለምን መንፈስ" ያንጸባርቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X