ፈረንሳይ የሳኅል ሀገራትን የሚያውኩ ቅጥረኛ ወታደሮችን ትደግፋለች - የኒጀር ፕሬዚዳንት
19:59 26.07.2026 (የተሻሻለ: 20:04 26.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፈረንሳይ የሳኅል ሀገራትን የሚያውኩ ቅጥረኛ ወታደሮችን ትደግፋለች - የኒጀር ፕሬዚዳንት
በቅርቡ በኒያሜ አየር መንገድ ላይ ጥቃት ያደረሱት አካላት በፈረንሳይ፣ በአውሮፓ ኅብረት ወይም በአጠቃላይ በምዕራባውያን የሚከፈላቸው ቅጥረኞች ናቸው ሲሉ አብዱራሃማኔ ቲያኒ ለመገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል።
ፈረንሳይ በጥር እና በሰኔ ወራት በአየር መንገዱ ላይ ለተፈጸሙት ጥቃቶች የገንዘብ፣ የሥልጠና እና የመሣሪያ ድጋፍ ማድረጓንም አብራርተዋል።
ፕሬዚዳንት ቲያኒ፤ ፓሪስ የመረጃ ጦርነት እያካሄደች ነው ሲሉ የከሰሱ ሲሆን ፈረንሳይ ከኒጀር ከመውጣቷ በፊት ኢማኑኤል ማክሮን ሀገሪቱ የነፃነት እና የመልካም አስተዳደር መንገድ በመምረጧ ምክንያት የሀገሪቱን ሉዓላዊ መንግሥት ለመጣል አቅደው ነበር ሲሉ አክለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X