ደቡብ አፍሪካ እና አፍሪካ በነፃነት መሳተፍ የሚችሉበትን የዲፕሎማሲያዊ ምህዳር መፍጠር አለባቸው - ደቡብ አፍሪካዊ ተንታኝ
09:59 26.07.2026 (የተሻሻለ: 10:04 26.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ደቡብ አፍሪካ እና አፍሪካ በነፃነት መሳተፍ የሚችሉበትን የዲፕሎማሲያዊ ምህዳር መፍጠር አለባቸው - ደቡብ አፍሪካዊ ተንታኝ
የደቡብ አፍሪካን ከቡድን 20 መገለል እና ከምዕራባውያን የበላይነት አወቃቀር ወደ ባለብዙ-ዋልታ ስርዓት የሚደረገውን ሽግግር በተመለከተ ለስፑትኒክ አፍሪካ አስተያየታቸውን የሰጡት የፖለቲካ እና ዓለም አቀፍ ጉዳዮች ተንታኟ ትሬሲ ሬይን፤ ፕሪቶሪያ እንደ ብሪክስ፣ የአፍሪካ ኅብረት እና የቡድን 20 ያሉ መድረኮች ላይ በንቃት ስትንቀሳቀስ የቆየችው የዲፕሎማሲ አማራጮቿን የማስፋት እና በአንድ ነጠላ ኃይል ላይ ያላትን ጥገኝነት የመቀነስ ግብ አንግባ ነበር ብለዋል።
ሆኖም የባለብዙ ዋልታ ስርዓት እኩልነትን እንደማያረጋግጥ እና የራሱ የሆኑ ግልጽ አደጋዎች እንዳሉት ሬይን አስጠንቅቀዋል።
መካከለኛ አቅም ያላቸው ሀገራት እርስ በርስ በሚፎካከሩ ቡድኖች በሚፈጠርባቸው ጫና ሊጠመዱ እንደሚችሉ እና ይህም አንዱን የበላይ ኃይል በሌላ የመተካት አደጋ ሊያስከትል እንደሚችል አመልክተዋል።
“ግቡ አንዱን የጂኦፖለቲካዊ አወቃቀር በሌላ መለወጥ ሳይሆን፤ ደቡብ አፍሪካ እና አፍሪካ በነፃነት ራሳቸውን የቻሉ ማዕከላት ሆነው እንዲሳተፉ በቂ የሆነ የዲፕሎማሲያዊ ምህዳር መፍጠር ነው” ብለዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X