የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ የአፍሪካን የኃይል ነፃነት ለማጠናከር ከግል ባለሀብቶች የገንዘብ ድጋፍ አገኘ
08:29 26.07.2026 (የተሻሻለ: 08:34 26.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የዳንጎቴ ነዳጅ ማጣሪያ የአፍሪካን የኃይል ነፃነት ለማጠናከር ከግል ባለሀብቶች የገንዘብ ድጋፍ አገኘ
የዳንጎቴ ግሩፕ በሌኪ፣ ናይጄሪያ የሚገኘውን የማጣሪያ ፋብሪካውን ማስፋፊያ ለመደገፍ፤ በአፍሪካ ትልቁ ይፋዊ የግል ኢንቨስትመንት ተብሎ በተገለጸው ሂደት 2.5 ቢሊዮን ዶላር ሰብስቧል።
ኩባንያው የአቅም ማስፋፊያ ፕሮግራሙን አጠናክሮ በሚገፋበት ወቅት ይህ ገንዘብ፤ የውስጥ የገንዘብ ፍሰቶችን እና የውጭ ፋይናንስን እንደሚደግፍ አሊኮ ዳንጎቴ ገልጸዋል።
ቀድሞውንም የአኅጉሪቱ ግዙፉ ማጣሪያ የሆነው ይህ ፋብሪካ፤ እ.ኤ.አ በ2028 የማምረት አቅሙን ከእጥፍ በላይ አሳድጎ በቀን ወደ 1.4 ሚሊዮን በርሜል ለማድረስ በወጠነው ዕቅድ፤ የህንዱን ጃምናጋር ፋብሪካ በመብለጥ በዓለም ግዙፉ ማጣሪያ ይሆናል።
ይህ ማስፋፊያ አፍሪካ ከውጭ በሚገቡ የተጣሩ ምርቶች ላይ ያላትን ጥገኝነት ለመቀነስ እና የአኅጉሪቱን የኃይል ደህንነት ለማጠናከር እንደሚያግዝ የዳንጎቴ ግሩፕ አስታውቋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X