የሱዳኑ አል-ቡርሃን አማፂውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይልና ደጋፊዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ዛቱ
18:44 25.07.2026 (የተሻሻለ: 18:54 25.07.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሱዳኑ አል-ቡርሃን አማፂውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይልና ደጋፊዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ዛቱ
"አማፂውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻ ከሀገር እናስወጣለን፤ ይህ መራራ ታሪክ ዳግም እንዳይደገም እናደርጋለን" ሲሉ አል-ቡርሃን በሰሜን ካርቱም በሚገኝ መስጂድ የጁምዓ ጸሎት ካደረሱ በኋላ ተናግረዋል። አክለውም፤ "ሚሊሻው እና እሱን የደገፉ እንዲሁም ከጀርባው የቆሙ አካላት ከዛሬ ጀምሮ ዳግመኛ በእግራቸው አይቆሙም" ብለዋል።
ከንግግራቸው የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
◻ የሱዳናውያንን ደም መመለስና መብታቸውን ማስከበር በምንም ዓይነት ድርድር የማይቀር ግዴታ መሆኑን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱ አስምረውበታል።
◻ በሰሜን ካርቱም የሚገኘው የሻምባት አካባቢ ነዋሪዎች ላሳዩት ጽናት እና ለመከላከያ ሠራዊቱ ላደረጉት ድጋፍ ምሥጋና አቅርበዋል።
◻ የጦር ኃይሉ አዛዥ ፈተናዎችን ለማለፍ እና በሀገሪቱ ሉዓላዊነት ላይ የተደቀኑ የውጭ ስጋቶችን ለመመከት የኅብረተሰቡ አንድነትና አብሮነት እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X