የሱዳኑ አል-ቡርሃን አማፂውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይልና ደጋፊዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ዛቱ

ሰብስክራይብ

የሱዳኑ አል-ቡርሃን አማፂውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይልና ደጋፊዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ ለማጥፋት ዛቱ

 

"አማፂውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻ ከሀገር እናስወጣለን፤ ይህ መራራ ታሪክ ዳግም እንዳይደገም እናደርጋለን" ሲሉ አል-ቡርሃን በሰሜን ካርቱም በሚገኝ መስጂድ የጁምዓ ጸሎት ካደረሱ በኋላ ተናግረዋል። አክለውም፤ "ሚሊሻው እና እሱን የደገፉ እንዲሁም ከጀርባው የቆሙ አካላት ከዛሬ ጀምሮ ዳግመኛ በእግራቸው አይቆሙም" ብለዋል።

ከንግግራቸው የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦

◻ የሱዳናውያንን ደም መመለስና መብታቸውን ማስከበር በምንም ዓይነት ድርድር የማይቀር ግዴታ መሆኑን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ፕሬዚዳንቱ አስምረውበታል።

◻ በሰሜን ካርቱም የሚገኘው የሻምባት አካባቢ ነዋሪዎች ላሳዩት ጽናት እና ለመከላከያ ሠራዊቱ ላደረጉት ድጋፍ ምሥጋና አቅርበዋል።

◻ የጦር ኃይሉ አዛዥ ፈተናዎችን ለማለፍ እና በሀገሪቱ ሉዓላዊነት ላይ የተደቀኑ የውጭ ስጋቶችን ለመመከት የኅብረተሰቡ አንድነትና አብሮነት እንዲጠናከር ጥሪ አቅርበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0