አሜሪካዊው የከባድ ሚዛን ቦክሰኛ የዓለም አትሌቲክስ ሩሲያን ማግለሉን በፅኑ ኮነነ

ሰብስክራይብ
አሜሪካዊው የከባድ ሚዛን ቦክሰኛ የዓለም አትሌቲክስ ሩሲያን ማግለሉን በፅኑ ኮነነ

ዴቪድ “ኒኖ” ሮድሪጌዝ የሩሲያ አትሌቶች በዓለም ላይ ካሉት ጠንካራ እና በጣም ሥርዓት ያላቸው አትሌቶች መካከል እንደሚመደቡ ገልጾ፣ እነሱን ማግለል የውድድሩን እንደሚያዳክም እና ፖለቲካ አሁንም ከስፖርት በላይ ቅድሚያ እንደሚሰጠው ማረጋገጫ ነው ሲል ተናግሯል።

የዓለም አትሌቲክስ በዚህ ወር በሩሲያ እና ቤላሩስ አትሌቶች ላይ የጣለውን ሙሉ እገዳ ያጠናከረ ሲሆን፣ ይህም የሆነው ዓለም አቀፉ ኦሊምፒክ ኮሚቴ በሩሲያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ላይ ጥሎት የነበረውን እገዳ በጊዜያዊነት ባነሳበት እና ለዓለም አቀፍ ስፖርት ፌዴሬሽኖች አስተላፎት የነበረውን የማግለል የውሳኔ ሐሳብ በሰረዘበት ወቅት ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
አዳዲስ ዜናዎች
0