የአዲሱ የዩክሬን ጦር ኃይሎች አዛዥ ሹመት ዐውደ-ግንባር ላይ ያለውን የውጊያ ሁኔታ ይለውጣል ተብሎ አይጠበቅም - ክሬምሊን
13:41 22.07.2026 (የተሻሻለ: 13:44 22.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአዲሱ የዩክሬን ጦር ኃይሎች አዛዥ ሹመት ዐውደ-ግንባር ላይ ያለውን የውጊያ ሁኔታ ይለውጣል ተብሎ አይጠበቅም - ክሬምሊን
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ የሰጧቸው ሌሎች መግለጫዎች፦
የኪዬቭ አገዛዝ ግልጽ አለመረጋጋት ይታይበታል፡፡
ኪዬቭ የውጊያ እንቅስቃሴዎችን በፍጥነት ለማቆም እና ወደ እውነተኛ ድርድር ለመሸጋገር ኃላፊነት የተሞላበት ውሳኔ ማድረግ ብቻ ነው የሚጠበቅባት፡፡
ፕሬዝዳንት ፑቲን በዩክሬን ያለውን ግጭት ለማቆም ከሁለት ዓመት በፊት ያስቀመጧቸው ቅድመ ሁኔታዎች ጸንተው የሚቀጥሉ ሲሆን ኪዬቭም ጠንቅቃ ታውቃቸዋለች፡፡
ሩሲያ በአሜሪካ በሚካሄደው የቡድን 20 ጉባኤ ላይ በከፍተኛ ደረጃ ተሳትፎ ታደርጋለች።
ቀደም ሲል፣ ዘለንስኪ የዩክሬን የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ኦሌክሳንደር ሲርስኪን ከኃላፊነት አንስተው፣ ሜጀር ጄነራል ሚካይሎ ድራፓቲይን በእሳቸው ምትክ ሾመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X