የሩሲያ ጥቃቶች የዩክሬንን የጥቁር ባሕር የወታደራዊ አቅርቦት ሰንሰለት መቱ - የመከላከያ ሚኒስቴር
20:09 21.07.2026 (የተሻሻለ: 20:14 21.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የሩሲያ ጥቃቶች የዩክሬንን የጥቁር ባሕር የወታደራዊ አቅርቦት ሰንሰለት መቱ - የመከላከያ ሚኒስቴር
የሩሲያ ኃይሎች ወደ ዩክሬን ወታደራዊ ጭነቶችን የሚያጓጉዙ የወደብ መሠረተ ልማቶችን እና መርከቦችን ዒላማ ማድረጋቸውን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር ገልጿል።
ወታደራዊ ጭነቶችን ለማውረድ እና ለማከማቸት ያገለግሉ የነበሩ የኦዴሳ ወደብ ተቋማት ተመትተዋል፡፡
በቸርኖሞርስክ ወደብ የሚገኝ የመርከብ ጥገና ማዕከል ጥቃት ተፈጽሞበታል፡፡
በኒኮላዬቭ ለዩክሬን ኃይሎች አቅርቦቶችን በማውረድ ላይ የነበረ የጭነት መርከብ ተመቷል፡፡
ቁሳቁሶችን ወደ ኦዴሳ እና ቸርኖሞርስክ ያጓጉዙ የነበሩ አንድ የደረቅ ጭነት መርከብ እና ሁለት ተጨማሪ የጭነት መርከቦችም ዒላማ ተደርገዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X