የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን በኒጀር እና ማሊ የተፈጸሙትን የሽብር ጥቃቶች በጽኑ ኮነነ
19:09 21.07.2026 (የተሻሻለ: 19:14 21.07.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የአፍሪካ ሕብረት ኮሚሽን በኒጀር እና ማሊ የተፈጸሙትን የሽብር ጥቃቶች በጽኑ ኮነነ
የሕብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር ማሕሙድ አሊ የሱፍ በኒጀር እና በማሊ የጦር ኃይሎች ላይ የተፈጸሙትን የሽብር ጥቃቶች በጽኑ አውግዘዋል።
በሳኅል ቀጣና እየጨመረ የመጣው የሽብር ጥቃት አሳሳቢ መሆኑን የጠቀሱት ሊቀመንበሩ፣ አገራት በመረጃ ልውውጥ፣ በድንበር ደኅንነት ቁጥጥር እና የሽብርተኞችን የፋይናንስ ምንጭ በመቁረጥ ረገድ ክልላዊ ትብብራቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
ማሕሙድ አሊ ለኒጀር እና ማሊ መንግሥታት፣ ሕዝቦች እና ለተጎጂ ቤተሰቦች የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸው፤ የአፍሪካ ሕብረት ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት ከወንድም አገራት ጎን እንደሚቆም አረጋግጠዋል።
ሊቀመንበሩ ሽብርተኝነትን በዘላቂነት ለመመከት አኅጉራዊ አንድነት፣ የተቀናጀ አሠራር እና አስተማማኝ የፋይናንስ አቅም መገንባት ወሳኝ መሆኑን አሳስበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X