የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለ500 ታዳጊዎች የሚሰጠውን 5ኛውን ዙር የክረምት የሠው ሠራሽ አስተውሎት ሥልጠና አስጀመረ

ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለ500 ታዳጊዎች የሚሰጠውን 5ኛውን ዙር የክረምት የሠው ሠራሽ አስተውሎት ሥልጠና አስጀመረ

ታዳጊዎቹ ለሁለት ወራት በሚቆየው በዚህ የ"ሰመር ካምፕ" ሥልጠና ስለ መሰረታዊ የኤ.አይ ክህሎት፣ ሮቦቲክስ፣ ዳታ ሳይንስ፣ ፕሮግራሚንግ እና ማሽን ለርኒንግ ከ50 በላይ በሚሆኑ የዘርፉ ባለሙያዎች በተግባር የተደገፈ ትምህርት እንደሚወስዱ ኢንስቲትዩቱ አስታውቋል።

የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር)፣ ሠው ሠራሽ አስተውሎት ሀገርና ትውልድን የሚቀይር መሆኑን በመጠቆም፣ ይህንን ታሳቢ ያደረገ የሰው ሠራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ በመገንባት ላይ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

ሥልጠናው በኢትዮጵያ የዲጂታል ለውጥ ጉዞ ውስጥ የነገውን ትውልድ በዘመናዊ እውቀትና ክህሎት ለመቅረጽ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተመልክቷል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0