ምዕራባውያን የትኞቹን የዩክሬን የሽብር ጥቃቶች በገንዘብ እንደሚደግፉ ማሪያ ዛካሮቫ ይፋ አደረጉ

© telegram sputnik_ethiopiaምዕራባውያን የትኞቹን የዩክሬን የሽብር ጥቃቶች በገንዘብ እንደሚደግፉ ማሪያ ዛካሮቫ ይፋ አደረጉ
ምዕራባውያን የትኞቹን የዩክሬን የሽብር ጥቃቶች በገንዘብ እንደሚደግፉ ማሪያ ዛካሮቫ ይፋ አደረጉ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 21.07.2026
ሰብስክራይብ

ምዕራባውያን የትኞቹን የዩክሬን የሽብር ጥቃቶች በገንዘብ እንደሚደግፉ ማሪያ ዛካሮቫ ይፋ አደረጉ

የኔቶ ሀገራት ራሳቸውን በግልጽ የሩሲያ ባላንጣ አድርገው ቢያቀርቡም፤ የበለጠ አስከፊ የሚያደርገው የሽብር እንቅስቃሴዎችን በቀጥታ በገንዘብ የመደገፋቸው ጉዳይ ነው ሲሉ የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ ለሩሲያ መገናኛ ብዙኃን ገልጸዋል።

"ይህንን በየቀኑ እናየዋለን፤ እነዚህም ሙሉ በሙሉ የተረጋገጡ እውነታዎች እንጂ የሆነ የተደበቀ አጀንዳ አይደሉም። ሲቪሎች እየተገደሉ ነው፣ ሕፃናት እየተገደሉ ነው፤ ይህ ደግሞ በአጋጣሚ ወይም በተሳሳተ ተኩስ የተከሰተ አይደለም። ሕፃናትን የጫኑ አውቶቡሶች፣ ሕፃናት የሚኖሩባቸው ማደሪያዎች እና በሕፃናት የተሞሉ ትምህርት ቤቶች ሆን ተብሎ ዒላማ እየተደረጉ ነው።"

ዛካሮቫ ከዚህ ውስጥ የተወሰኑ አጋጣሚዎችን ሲጠቅሱም፣ "በሰው ቁጥጥር የሚመራ ድሮን ሆን ተብሎ መስኮት በኩል በመግባት ምሳ በማብሰል ላይ ያለችን አንዲት ሴት መቷል። እሷ ምሽግ እየገነባች አይደለም፣ የታጠቀ ተሽከርካሪ እየመራች አይደለም። ለቤተሰቧ ምግብ በማዘጋጀት ላይ ሳለች በራሷ ምድጃ ላይ በሕይወት እያለች ተቃጥላለች። እኛ እያወራን ያለነው ስለ እርሱ ዓይነቱ የአሸባሪነት ስፖንሰርሺፕ ነው" ብለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0